Category "Latest News"

ብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ሥጋትን በልማት ዕቅድ ሒደቶችና በኢንቨስትመንት ውሳኔዎች ውስጥ አካቶ ለማስፈጸም የሚያግዝ መመርያ ይፋ አደረገ፡፡ መመርያው በተለያዩ የአስተዳደር እርከኖችና የልማት ደረጃዎች የሚገኙ የፌዴራል፣ የክልል፣ የወረዳ፣ የቀበሌና የከተማ አስተዳደር አካላት የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያና የምላሽ ሥርዓቶችን በሁሉም የመንግሥት መዋቅሮች ውስጥ አካተው እንዲፈጸሙ የወጣ መሆኑ ታውቋል፡፡

የስትራቴጂውን ዓላማ ለማስፈጸምም የአደጋ ሥጋት አመራርን በአግባቡ ለመተግበር የሚያስችል የተመቻቸ ሁኔታ መፍጠር፣ ዘርፈ ብዙ የአቅም ግንባታና ዓለም አቀፍ የማቴሪያልና የገንዘብ ድጋፎችን ማቀናጀት ግድ መሆኑ በመመርያው ሠፍሯል፡፡ የአደጋ ሥጋትን በልማት ዕቅዶች ውስጥ በማካተት የመተግበርን አሠራር መስመር ለማስያዝ የተዘጋጀው ይህ መመርያ ይፋ የተደረገው፣ ረቡዕ መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል በተዘጋጀው መድረክ ነው፡፡

የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራርን፣ በመደበኛ የሥራ እንቅስቃሴያቸው ውስጥ በማካተት መተግበር እንዳለባቸውም ታውቋል፡፡ የአደጋ ሥጋት ፖሊሲና ስትራቴጂ የልማት ፕሮግራሞች በልማት ማዕቀፎች፣ በተለይም በመንግሥት፣ በግልና በማኅበረሰብ አቀፍ ልማት ዕቅዶች ውስጥ ተካተው እንዲፈጽሙ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ይህም የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራርን አካቶ መተግበር፣ የሥጋት ዳሰሳ ማድረግና መከላከልን የተመለከተ እንደሆነ፣ አሠራሩም ከላይኛው የመንግሥት እርከን እስከ ታችኛው ድረስ በተለያዩ የልማት እንቅስቃሴዎች መቀየር እንዳለባቸው ያመለክታል፡፡

የብሔራዊ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽንም የስትራቴጂካዊ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ ማዕቀፍ በማዘጋጀት፣ የተለያዩ የአደጋ ሥጋት ቅነሳ ፕሮግራሞችንና ስትራቴጂዎችን በመቅረፅ ወደ ሥራ መግባቱ ተገልጿል፡፡ ከተጀመሩት ፕሮግራሞች ዋነኛውም የወረዳ አደጋ ሥጋት ተጋላጭነት ፕሮፋይል ጥናት ነው፡፡ ጥናቱ በወረዳዎች የሚታየውን የአደጋ ተጋላጭነት፣ ክስተት፣ አቅም፣ መንስዔዎችን ለተለያዩ የአደጋ ቅነሳ ሥራዎች መነሻ መረጃ ያቀብላል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሁሉም የአገሪቱ ገጠራማ ወረዳዎች የተጋላጭነት ፕሮፋይል ጥናት እየተካሄደ መሆኑን፣ የ455 ወረዳዎች ፕሮፋይል መጠናቀቁ ተጠቁሟል፡፡

ኢትዮጵያ በተለይም በድርቅ ምክንያት ሊከሰት የሚችል የኢኮኖሚ ጉዳት ለመቀነስ የሚያስችል አቅም በመፍጠር ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው የተሻለ መሥራት ብትችልም፣ እየተከሰቱ ያሉ ሰው ሠራሽ አደጋዎች ድርብ ፈተና እንደሆኑባት ይታወቃል፡፡ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት እየተስተዋለ ያሉ ግጭቶችና የዜጎች መፈናቀሎች በኢኮኖሚው ላይ እያደረሱ ያለው ተፅዕኖ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል፡፡

ባለፉት ወራት ተቀስቅሶ በነበረው የጌዴኦና የምዕራብ ጉጂ ግጭት ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከቀዬአቸው ተፈናቅለዋል፡፡ በቡራዩ ዙሪያ በሚኖሩ ወገኖች ላይ በተፈጸመ ጥቃት በርካቶች ቤት ንብረታቸውን መልቀቃቸው ይታወሳል፡፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተቀሰቀሰው ግጭትም በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቅለዋል፡፡ በጥቂት ወራት ውስጥ በተከሰተው የአገር ውስጥ መፈናቀል ሚሊዮኖች ለጉዳት ተዳርገዋል፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩም ሕይታቸውን አጥተዋል፡፡

‹‹ለአደጋ ያለን ተጋላጭነት በአየር ንብረት ለውጥም ሆነ በውስጥ ግጭቶች እየጨመረ መጥቷል፤›› ያሉት በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የድንገተኛ ጤና አደጋዎች አማካሪ አቶ አስቻለው በላይነህ ናቸው፡፡

ከባለ ድርሻ አካላት መካከል የሆነው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሥሩ ከሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር ለሚከሰቱ አደጋዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠት የሚያስችለውን አሠራር እየተከተለ መሆኑ ታውቋል፡፡ ሐኪሞችን ጨምሮ የተለያዩ የሕክምና ባለሙያዎቸን ያካተተ ‹‹የአደጋ አመራር አጋዥ ቡድን›› የተባለ ግብረ ኃይል በየሆስፒታሉ ከማዘጋጀት ጀምሮ፣ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለአጣዳፊና እንደ ስኳርና ደም ግፊት ላሉ በሽታዎች የሚሆኑ 78 ዓይነት መድኃኒቶችን የሚይዝ ‹ኪት› በማዘጋጀት አደጋ በተከሰቱባቸው ቦታዎች እንዲደርሱ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በአገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ሰው ሠራሽ አደጋ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቆጣጠር ፋታ የነሳ ይመስላል፡፡ ‹‹ዕርዳታ ሕመም ማስታገሻ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ አይሆንም፤›› ያሉት ኮሚሽነሩ አቶ ምትኩ ካሳ፣ እንደ ድርቅ ያሉ የተፈጥሮ አደጋዎችን መቋቋም የሚያስችል ዘለቄታዊነት ያለው መፍትሔ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡ በአገሪቱ የሚተዋሉ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች የሚያደርሱትን ተፅዕኖ ለመቀነስም፣ የባለድርሻ አካላት ትብብር ግድ እንደሚል ኮሚሽነሩ አስረድተዋል፡፡

ሪፖርተር

More than 106 participants comprised from government, NGO’s, private & societies gather to discuss Addis Ababa resilient challenge.The discussion with multilateral stakeholders was to make the city Resilient to shock and stress. The Consultative Workshop was held on October 11 – 12, 2018 at Friendship International Hotel in Addis Ababa.

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን በየቀኑ በሚያመርተው ውኃና በፍላጎት መካከል ከፍተኛ ልዩነት በመፈጠሩ፣ በይፋ ወደ ፈረቃ አሠራር መግባቱን አስታወቀ፡፡
ባለሥልጣኑ በአሁኑ ወቅት ከገጸ ምድርና ከከርሰ ምድር በቀን የማምረት አቅሙ 525 ሺሕ ሜትር ኩብ ውኃ ነው፡፡ ነገር ግን ከተማው የሚፈልገው የውኃ መጠን በቀን ከ930 ሺሕ እስከ አንድ ሚሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
በአቅርቦትና በፍላጎት መካከል ካለው ከፍተኛ ልዩነት በተጨማሪ፣ የተመረተው ውኃ ሙሉ በሙሉ ለነዋሪዎች እንዳይደርስ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና የቴክኒክ ብልሽቶች ምክንያት መሆናቸው ታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን አባተ (ኢንጂነር) ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ቢያንስ በ12 እና በ24 ሰዓት ልዩነት ውኃ ያገኙ የነበሩ አካባቢዎች፣ አሁን እስከ አሥራ ሶስት ቀናት ድረስ ይዘገይባቸዋል፡፡
‹‹በአዲስ አበባ በተለያዩ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጦች ላይ የሚገኙ አካባቢዎች ስላሉና ነዋሪዎችም በምድርና በሕንፃ ውስጥ የሚኖሩ ስለሆኑ፣ ቢያንስ በሳምንት ሦስት ጊዜ ውኃ ለማዳረስ ይሠራል፤›› ሲሉ ዋና ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡
እሳቸው እንደሚሉት፣ የክረምት ወራት በቅርቡ የወጣ እንደመሆኑ ግድቦች መያዝ ያለባቸውን የውኃ መጠን ይዘዋል፡፡ ‹‹ነገር ግን ከተማው እየሰፋ በመሄዱ ውኃ በብዛት የሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ ስለሆነ፣ የውኃ ፍላጎት እየጨመረ ነው፤›› ብለዋል፡፡
‹‹የአጭር ጊዜ ዕቅድ በፈረቃ ማድረስ ቢሆንም፣ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ስለሆነ በፍጥነት በማጠናቀቅ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሠራ ነው፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡
የተወሰኑ ሠራተኞች ለችግሩ መባባስ አሻጥር ይሠራሉ እየተባለ ስለሚነገረው ጉዳይ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ጥያቄ ቀርቦላቸው ሲመልሱ የባለሥልጣኑ ሠራተኞች መልካም መሆናቸውን፣ የተወሰኑ ሠራተኞች ግን በዚህ ዓይነት ድርጊት የተሠማሩ ስለመሆኑ ሲነገር እንደሚሰማ፣ ዕርምጃ መውሰድ የሚያስችል ማስረጃ ግን እንደሌለ አስረድተዋል፡፡
ሪፖርተር

ከአገር ኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ተያይዞ የኬሚካሎች ዝውውርና ክምችት እየተስፋፋ በመሄዱ፣ የተለያዩ ኬሚካሎች ብክለት ሥጋት እየጨመረ እንደመጣ ተገለጸ፡፡
ይህ የተገለጸው ማክሰኞ መስከረም 29 ቀን 2011 ዓ.ም. በጁፒተር ሆቴል በተከፈተው ዓለም አቀፍ የኬሚካል ደኅንነትና አስተዳደር ጉባዔ ላይ ነው፡፡ ዓለም አቀፍ የኬሚካል መሣሪያዎች መከላከል ድርጅት ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ በማካሄድ ላይ ባለው ሥልጠና፣ አገሮች ጅምላ ጨራሽ ኬሚካል መሣሪያዎችንና አደገኛ ኬሚካሎችን እንዴት መቆጣጠር እንደሚችሉ ሰፊ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡ በሥልጠናው ላይ የታሰተፉ ባለሙያዎች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኬሚካል መሣሪያዎች ዝውውር በኢትዮጵያ አሳሳቢ ባይሆንም ከግብርና ቴክኖሎጂዎችና አምራች ኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር የአደገኛ ኬሚካሎች ብክለት ሥጋት እየጨመረ መጥቷል፡፡ አሳሳቢ የሆኑ የኬሚካል ብክለት ሥጋቶች በሁለት መንገዶች እንደተጋረጡ ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡

አንደኛ ለተለያዩ አገልግሎቶች ወደ አገር ውስጥ ገብተው የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸው ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ናቸው፡፡ እነዚህ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ፀረ ተባይ፣ ፀረ አረም፣ ማዳበሪያዎችና ሌሎች የተለያዩ ኬሚካሎች ሲሆኑ፣ በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች ተከማችተው ይገኛሉ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥቅም ላይ እንዳይውል የተከለከለው ዲዲቲ ብቻ ከ1,400 ቶን በላይ በአዲስ አበባ፣ በአዳማና በሐዋሳ ከተሞች ተከማችቶ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ የአደገኛ ኬሚካሎች አስተዳደርና አወጋገድ ሥርዓት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያልነበረ በመሆኑ፣ በማንና እንዴት እንደገቡ የሚገልጽ ሰነድ የሌላቸው በርካታ አደገኛ ኬሚካሎች በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ተከማችተው እንደሚገኙ ባለሙያዎቹ አስረድተዋል፡፡
የኬሚካሎች ምዝገባ፣ የአወጋገድ ሥርዓትና ማስወገጃ ተቋም ወይም ቦታ ባለመኖሩ እነዚህ ኬሚካሎች ለማኅበረሰብ ጤናና አካባቢ አደገኞች ናቸው ተብሏል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ የተጠቀሰው ብክለት ከተለያዩ ፋብሪካዎች በሚወጡ ዝቃጮች ነው፡፡ በተለይ ከቆዳ፣ ከቀለምና ከጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች የሚወጡ እንደ ሜርኩሪና ሊድ ያሉ ከባድ ብረቶች ወንዝ ውስጥ በመግባት፣ በሰው ልጅ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርሱ ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡

በአዲስ አበባና በአካባቢዋ የሚገኙ የቆዳና የቀለም ፋብሪካዎች ከውኃ ጋር ተቀላቅለው የሚወጡ አደገኛ ኬሚካሎችን ወደ ወንዞች በመላክ፣ በአካባቢና የሰው ልጆች ላይ ከፍተኛ ቀውስ በመፍጠር ላይ እንደሆኑ ይገልጻሉ፡፡ እነዚህ እንደ ሜርኩሪና ሊድ ያሉ በውኃና አፈር ውስጥ ገብተው ለረዥም ጊዜ መቆየት የሚችሉ አደገኛ ኬሚካሎች ካንሰር ሊያመጡ እንደሚችሉ፣ በተለይ በአቃቂ ወንዝ ላይ ከፍተኛ ብክለት እየተከሰተ በመሆኑ ናሙና ተወስዶ ምርምር ሊካሄድ እንደሚገባ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ ወንዞች ዳርቻ የሚመረቱ አትክልቶች ጉዳይ ትልቅ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑን ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡

በስብስባው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዮሐንስ ድንቃየሁ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ የአገልግሎት ጊዜ ያለፈባቸው አደገኛ ኬሚካሎች በአገር ውስጥ ሊወገዱ አይችሉም፡፡ ኬሚካሎቹ ሊወገዱ የሚችሉት ወደተመረቱበት አገር ተልከው እንደሆነ የገለጹት አቶ ዮሐንስ፣ ይህን ለማድረግ በጀት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ በተከማቹ ኬሚካሎች ላይ የሚሠራ ግብረ ኃይል በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስተባባሪነት መቋቋሙን የገለጹት አቶ ዮሐንስ፣ ኬሚካሎቹ የት እንደሚገኙና ዓይነታቸውና መጠናቸውን ለይቶ ኬሚካሎቹን ለማስወገድ የሚያስፈልገው የበጀት መጠን አጥንቶ ለማቅረብ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከግብርናና እንስሳት ሀብት ሚኒስቴርና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተባብሮ በመሥራት ላይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ሃላላ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በኬሚካል ምርት አጠቃቀምና ዝውውር ላይ ቁጥጥር ለማካሄድ የሚያስችል የኢንዱስትሪ ኬሚካል ምዝገባና አስተዳደር አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ወጥቷል፡፡ በአካባቢ፣ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስቴር የተረቀቀው አዋጅ ከውጭ የሚገቡና በአገር ውስጥ የሚመረቱ ኬሚካሎች በማዕከልነት መመዝገብና መቆጣጠር የሚያስችል እንደሆነ የገለጹት አቶ ሳሙኤል፣ በቀጣይ ደንቦችና መመርያዎች ወጥተውለት ሥራ ላይ እንደሚውል ተናግረዋል፡፡
‹‹ኬሚካሎችን የመከታተልና መቆጣጠር ኃላፊነት ለኢንስቲትዩቱ የተሰጠ በመሆኑ ከአካባቢ፣ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ለመሥራት በዝግጅት ላይ ነን፤›› ብለዋል፡፡ ይህ ትልቅ ኃላፊነት የተጣለበት የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የኬሚካል ምርመራዎች የሚያካሂድበት አንድም ቤተ ሙከራ እንደሌለው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ከተመሠረተ አራት ዓመታት የሆነውና ትልቅ አገራዊ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም ቤተ ሙከራ የሌለው በመሆኑ ሥራውን በብቃት ለመወጣት እንደሚቸገር ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡
አቶ ሳሙኤል ለትችቱ በሰጡት ምላሽ ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ቤተ ሙከራዎችን እንደሚጠቀም ገልጸው፣ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተሰጠ መመርያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚሰጣቸው ቦታ የዋና መሥሪያ ቤትና የቤተ ሙከራ ሕንፃ መገንባት እንደሚጀምር ገልጸዋል፡፡ በአገሪቱ ተከስቶ በነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት የአዲስ አበባ አስተዳደር የግንባታ ቦታ ለማዘጋጀት ተስኖት እንደነበር ገልጸው፣ ይህ ችግር አሁን በመቀረፉ ቦታው ተዘጋጅቶ ወደ ግንባታ እንደሚገባ ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል፡፡
‹‹የኢንስቲትዩቱን አቅም እንገነባለን፡፡ የራሳችን ቤተ ሙከራም ይኖረናል፡፡ እስካሁን ግን የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችን ቤተ ሙከራዎች ስለምንጠቀም፣ የቤተ ሙከራ አለመኖር ሥራችንን ከመሥራት አያግደንም፤›› ብለዋል፡፡
ሪፖርተር

Ethiopia has launched a 10 year National Forest Sector Development Program (NFSDP) targeted to serve as the main guiding document for coordinating strategic policy interventions.The Program is launched by the Ministry of Environment Forest and Climate Change (MEFCC) in collaboration with UNDP.
Launching the program, Minister of MEFCC Gemedo Dalle said the climate resilient Green Economy (CRGE) recognizes that deforestation and forest degradation must be reversed if the country is to meet its development goals.Therefore, Ethiopia has set triple goal of attaining middle income status while pursuing net-zero emission economic growth and building resilience by 2025, he said.
“Ethiopia`s Ten Years National Forest Sector Development Program together with other initiatives, we are launching today, will serve as roadmap for coordinating strategic policy interventions and sector wide investments,” Gemedo noted.
He stated that the program contains transformational action programs for catalyzing GDP, generating employment, and contributing towards self-sufficiency in forest products.UNDP Country director Louise Chamberlain said on her part that the goal of the plan can only be achieved with strong involvement of the people of Ethiopia and government leaders at all levels and across the country through strong partnerships.
The NFSDP will ensure an increase in Ethiopia`s forest coverage to 20 percent in 2020 and 30 percent in 2025 and make forest a core sector in economic structural reforms.It will also be a major source of income for people living in rural areas, diversifying income for small holder farming households, she stated.
A UNDP Study showed that, the forest contribution to GDP is 12 percent as opposed to 2-4 percent in the current GDP calculation for the forest sector.Ethiopia`s forest coverage has reached to 15.5 percent currently.
Source-ENA

The Federal Transport Authority announced on septembre 25/2018 that it has launched electronic service (e-service) to deliver 18 online services.E-Service is an electronic form of public service provision.
Using the e-Service system developed in cooperation with Ministry of Communications and Information Technology, government organizations can render electronic public services to citizens, non-citizens, businesses, governmental and non-governmental organizations.

Speaking at the official launching ceremony, Federal Transport Authority Director-General Abdissa Yadeta said the transport sector creates social linkages and supports economic development, but delivering swift and modern service was challenging.
The e-Service would facilitate modern service delivery and solve maladministration, the director-general added.According to Abdissa, “anybody with Internet access and computer or mobile device can register online and request the services from anywhere.”
Communications and Information Technology State Minister, Sisay Tolla said implementing the electronic service would solve various customer related problems.Sisay stated that electronic service reduces direct human interaction, stores documents properly, enhances transparency and accountability, simplifies processes, increases productivity, and prevents corrupt practices.
To file a service request, users would login on www.eservices.gov.et using her/his account or can register in the system to get a user account and continue with his/her application.The online services cover vehicle quality assurance and import, cargo transport, and public transport.
Source-ENA

በአዋሽ ወንዝ ሙላት እንደሚደርስ የተገመተው የጎርፍ አደጋ ስጋት መቀነሱን የአዋሽ ተፋሰስ የጎርፍ መከላከል ግብረ ኃይል አስታወቀ።ከሳምንታት በፊት በፌዴራል ደረጃ የተዋቀረው የአዋሽ ተፋሰስ የጎርፍ መከላከል ግብረ ኃይል በአፋር ክልል በሚገኙ የታችኛውና መካከለኛው አዋሽ ተፋሰስ የስጋት ስፍራዎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።ግብረ ኃይሉ የጉብኝቱን ማጠቃለያ ግምገማ አስመልክቶ ለኢዜአ እንደገለጸው በአዋሽ ተፋሰስ ይደርሳል ተብሎ የተጠበቀው የጎርፍ አደጋ ስጋት መቀነሱን አረጋግጧል።

አዋሽ በአገሪቱ ከሚገኙ 12 ተፋሰሶች በስፋት የለማና በተፈጥሯዊ የተፋሰስ ባህሪም በክረምት ወቅት ከፍተኛ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሚከሰትበት ነው።በዘንድሮ ክረምት በነበረው ከፍተኛ የዝናብ መጠን ትንበያና በአዋሽ ተፋሰስ በሚገኙ ግድቦች ሙላት ሳቢያ በተፋሰሱ የጎርፍ አደጋ እንደሚደርስ ስጋት አሳድሮ ነበር።

ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስም በፌዴራል፣ በኦሮሚያና በአፋር ክልሎች የሚገኙ ባለድርሻ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ያካተተ የጎርፍ መከላከል ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ወደስራ ተገብቷል።በብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚመራውና ብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂን፣ ውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክና መከላከያ ሚኒስቴሮችን፣፣ አዋሽ ተፋሰስ ባለስልጣን፣ የኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን፣ ስኳር ኮርፖሬሽን፣ የአፋርና የኦሮሚያ ክልል የአደጋ ስጋት መከላከል ቢሮዎችና ሌሎች ተቋማትን በአባልነት ያቀፈው ግብረ ኃይሉ ለሁለት ቀናት በአፋር ክልል የተፋሰሱን አካባቢዎች ጎብኝቷል።

ከአዋሽ ተፋሰስ ስፍራዎች መካከልም በታችኛው አዋሽ ዱብቲ ወረዳና የተንዳሆ ግድብን፣ በመካከለኛው አዋሽ ደግሞ የገዋኔ፣ አሚባራና አዋሽ ፈንታሌ ወረዳዎች በሚገኙ የአዋሽ ወንዝ የስጋት ቦታዎች እንዲሁም የከሰም ግድብን ተመልክቷል።የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክትል ኮሚሽነር ዳመነ ዳሮታ እንዳሉት በጉብኝቱ በአዋሽ ተፋሰስ ባለስልጣን የተከናወኑ አበረታች የጎርፍ መከላከል ስራዎችና በአንዳንድ ቦታዎች የአዋሽ ወንዝ መስመሩን ሰብሮ በእርሻ ልማት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተስተውሏል።

“ውሃ በአግባቡ ከተመራ መልካም እድል ነው” ያሉት አቶ ዳመነ አዋሽ ወንዝ “በክረምት ሽሽት፣ በበጋ ደግሞ የውሃ እጥረት” የሚስተዋልበት ተፋሰስ እንደሆነ በማንሳት ጉብኝቱ በመናበብ፣ በቅንጅትና በባለቤትነት ከተሰራ አደጋን መቋቋም እንደሚቻል ያመላካተ ነው ብለዋል።

ቀደም ሲል በላይኛው አዋሽ ተፋሰስ የመስክ ምልከታ መደረጉን አንስተው በመካከለኛውና በታችኛው ተፋሰሱ የተከናወኑ የቅደመ መከላከል ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የግብረ ኃይሉ አባላት ኃላፊነት ወስደዋል ነው ያሉት።የአዋሽ ተፋሰስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ግዛውም 80 በመቶው የአዋሽ ተፋሰስ ለጎርፍ አደጋ የተጋለጠ መሆኑን ገልጸው፤ ከጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭ ያልሆነው የተፋሰሱ ክፍል ከ18 በመቶ እንደማይበልጥ ተናግረዋል።

በዘንድሮው ክረምት ቀደም ሲል በብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂ ትንበያ መሰረት ባለስልጣኑ ለጎርፍ አደጋ እጅግ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ከ300 ኪሎ ሜትር በላይ የጎርፍ መከላከያ ዱካዎችን የመስራት፣ ነባሩን የማስተካከልና የመጠገን ስራዎች መስራቱን ገልጸዋል።

ከከሰም በስተቀር የቆቃና ተንዳሆ ግድቦች ከሚፈለገው መጠን በላይ ሞልተው አደጋ እንዳያደርሱ የውሃ መጠን የማስተንፈስ ስራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።ለጎርፍ አዳጋ ስጋት የነበረው የከሰም ግድብም አሁን ላይ መጠኑ እየቀነሰ በመሆኑ ይደርሳል የተባለው የአደጋ ስጋት መቀነሱን ነው ያብራሩት።

የአዋሽ ወንዝ ከአራት ዓመታት በፊት ሞልቶ ጉዳት ያደረሰው መስከረም 28 እንደነበር በማውሳት መስከረም የክረምት አካል በመሆኑ አሁንም ጥንቃቄ የሚፈልጉ ስራዎች መከናወን እንዳለባቸው የስራ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል።ከክረምት ወራት ሙሉ በሙሉ ተወጥቷል ባይባልም በግብረ ኃይሉ ግምገማ ግን ከዚህ በኋላ በተፋሰሱ የከፋ ጉዳት ይኖራል የሚል ስጋት እንደሌለ ነው የገለጹት።

አቶ ዳመነ ዳሮታ እንደተናገሩት ከዚህ ቦኃላ የከፋ ስጋት እንደማይመጣና ነገር ግን ትኩረት አድርጎ ለመስራት ኃላፊነት በመውሰድ በቆይጣቸው አስቀምጠዋል፡፡አቶ ጌታቸው ግዛው በበኩላቸው በዚህ ክረምት ከነበረው ጠንካራ የክረምት ዝናብ አንጻር ቀደም ብለን ያደረግናቸው በቂ ዝግጅቶች ሊደርስ የሚችለውን አደጋ መቋቋም ማስቻሉንና አሁንም የግብረ ኃይሉ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ነው ብለዋል፡፡

ኢዜአ

 

Ethiopia currently has 180,000ha of forest cover. The government projects to increase this by five percent within two years. The nation is gearing up to adopt a new 10-year master plan for sustainable forest management.
The draft master plan, National Forest Sector Development Program, is developed by the Ministry of Environment, Forest & Climate Change and has five principal pillars – enabling environment and institutional development, sustainable forest production and value chain, forest environmental services, forests and rural livelihoods, and urban greening and urban foresting.
The master plan envisions the reforestation of nearly 2.5 million hectares of land with tree plantations, the creation of over 600,000 full-time jobs, increasing the value of agriculture and other sectors by 3.2 billion dollars and fully substituting the import of wood products.
The plan is intended to be used by regional states as a blueprint to formulate their own programs to lower carbon emissions into the atmosphere by 50pc.
“It will be the principal policy document in coordinating strategic interventions and directing sector-wide investments for the next 10 years,” said Tefera Mengistu (PhD), coordinator at the Ministry’s Forest Sector Development Program.
To attain the goals of the national forestry plan, roughly 15 billion dollars in investment are needed, and the plan is to target and leverage growing global interest to reduce deforestation and improve the management of existing forest resources.
The United Nations Development Programme, and the governments of Norway and Sweden have already pledged 10.5 million dollars and 6.5 million dollars, respectively.
“The local demand for forest products has increased over the past years,” Tefera said, explaining the need for the new master plan. “Besides, the global phenomenon of climate change needs to be addressed strategically.”
The plan replaces the Ethiopian Forestry Action Program, which has been in place since 1994.
“As Ethiopia continues to experience rapid economic growth, the demand for timber, non-timber forest products and environmental services increases, making the role forestry plays in the economy more important and relevant,” said Ababu Anage, national climate change specialist at the UN agency.
Currently, Ethiopia has 180,000ha of land under forest cover, and the government plans to increase this figure by five percent by the end of 2020. To attain its current demand for timber, Ethiopia has to develop about 310,000ha of new commercial forest plantation.
“We have to create well-managed commercial forests,” argues Tefera. “To attain this, we need to invite the private sector to engage in the forest industry.”
To reach this target, the master plan envisages the establishment of new commercial plantations, tree planting in the form of small-scale woodlots, afforestation, reforestation and forest landscape restoration.
The plan is also aligned with the Climate-Resilient Green Economy strategy, according to Ababu.
“Protecting and re-establishing forests for their economic and ecosystem services is one of its main stakes,” he said.
The project aims to double the contribution of the industry to the country’s gross domestic product by 2020, which currently stands at four percent.
“Forestry is a missed opportunity in Ethiopia,” said Mulugeta Limenih (PhD), an expert on forestry with over a decade experience, at a press conference organised by the Ethiopian Forestry Society. “There is very little public investment in forest development, and private players are not attracted to it.”
Ethiopia needs to have a long-term strategy and a robust institutional environment, he added.
Ethiopia’s natural forests and woodlands hold various commercially essential forest products, according to the report.
Ethiopia’s forests generated economic benefits in the form of cash and in-kind income equivalent to 16.7 billion dollars in 2012. Over the past decade, Ethiopia imported over 1.1 billion dollars worth of wood and wood products.

Source-Fortune

Addis Ababa is moderately polluted and that is a major environmental risk which could affect sensitive people, Environment, Forest and Climate Change (MEFCC) State Minister Negusu Lemma disclosed.

Speaking at the Air Quality Management Workshop that opened  in Sptember 17/2018 at addis ababa, the State Minister said “97 percent of cities in low and middle income countries with more than 100,000 inhabitants do not meet the World Health Organization air quality guidelines.”

Addis Ababa Environmental Protection Agency General Manager, Alemi Asefa said on her part old cars with high gas emission rate, and gas from solid wastes released especially by constructions and industries are mainly aggravating pollution in the city.

According to her, the US Environmental Protection Agency Air Quality Management Plan that will be delivered in early 2019 helps to identify major air pollution sources, general status of the city and its health and economic impacts.

US Charge d’affaires Troy Fitrell said US and Ethiopia will work in partnership to improve air quality management to build healthy environment and population in the country.

“The US believes that an investment in improving Ethiopia’s air quality is an investment worth making because clean air is not leisure, it is a necessity we cannot live without,” Fitrell added.

The Workshop discussed various aspects of air quality management, policies and sources.

Source-ENA

 

Collaboration Workshop (CoLab) on Building a Water Resilient City Convenes Partners, Subject Matter Advisors, and City Representatives to Drive Innovation and Introduce Pathways to Enhance Urban Resilience

CoLab Precedes Launch of City’s Preliminary Resilience Assessment and Feeds into Development of Comprehensive Resilience StrategyCape Town, South Africa – In the context of a partnership toward building a more resilient Cape Town, 100 Resilient Cities – Pioneered by The Rockefeller Foundation (100RC) is hosting a Collaboration Workshop (CoLab) on Building a Water Resilient City this week. The CoLab, to be attended by international partners and experts, representatives from city governments, and other member cities from the 100RC global network, will take a cross-sectoral approach to building and identifying innovative and collaborative solutions and practices needed to bridge gaps endemic to highly complex, systemic urban issues. The CoLab runs September 18-20 at GreenCape, a sector development organisation funded by the City of Cape Town.

This is the first CoLab to be run in Africa, building off of previous workshops on economic development, school infrastructure, and public transportation held over the past year in cities across Europe, South America, and North America.

The multi-year drought shock that Cape Town is currently experiencing is an opportunity to more comprehensively think about water system resilience and to catalyse change through introducing alternative, resilient pathways guided by sustainability. The CoLab is expected to drive innovation and identify solutions toward fortifying the resilience of Cape Town’s water system and the city’s wider resilience for years to come.

“Cape Town has shown certain characteristics of resilience during the drought, but much more needs to be done before we can truly regard Cape Town as a water resilient city. What the City of Cape Town and its people have achieved during the drought is remarkable, but we must ensure that the lessons we learnt during the drought are retained, and make us better prepared for future shock events,” said Councillor Xanthea Limberg, Mayoral Committee Member for Informal Settlements, Water and Waste Services.

“Cape Town is not alone: water-related hazards like floods, droughts, pollution, and related issues are increasing in frequency and intensity, impacting more than 80% of 100RC member cities worldwide,” said Liz Agbor-Tabi, Associate Director for City Resilience Delivery at 100 Resilient Cities. “The CoLab is a unique opportunity to explore how water ties into Cape Town’s larger social, economic, and political ecosystem – with the aim of fostering a stronger, more resilient city.”

A 100RC CoLab is a collaborative, expedited process between municipal government, subject matter experts, and members of the 100RC Platform of Partners. The 100RC Platform is a curated suite of resilience-building tools and services, provided by partners from the private, public, academic, and non-profit sectors at no direct cost to member cities. 100RC Partners at the Cape Town CoLab include: Arup, Deltares, Deutsche Gesellschaft für Internationale Zusammenarbeit (GIZ) GmbH, The Nature Conservancy, Swiss Re, Veolia, and WWF South Africa, with additional collaboration from the SA SDI Alliance and The Resilience Shift. Also attending the event to contribute their cities’ experience are representatives from fellow 100RC members Los Angeles, Mexico City, and Addis Ababa.

The City of Cape Town is currently in the process of developing its first Resilience Strategy with support from 100 Resilient Cities. The City will launch its Preliminary Resilience Assessment, a robust analysis of Cape Town’s resilience opportunities and challenges, on Friday. Findings reveal drought, rainfall flooding, unemployment, and substance abuse as top concerns among more than 150 thematic specialists consulted and over 11 000 residents surveyed in the months-long assessment process. Challenges incorporate one-time shock events as well as stresses that weaken the urban fabric on a day to day or cyclical basis.

“Water management is a crucial component of Cape Town’s resilience-building process, but it cannot be addressed in a silo,” said Gareth Morgan, Director of Resilience in the City of Cape Town’s Corporate Services Directorate. “Our city’s vulnerability to climate shocks has distinct implications for a growing population shouldering high rates of unemployment, poverty, and a lack of affordable housing. Although daunting, these challenges are also our greatest opportunities.”

The CoLab will explore the impacts of drought and water insecurity on the city’s resilience, understand underlying causes and barriers, and utilise the collective experience and knowledge of the local and international participants to develop concrete courses of action – to help Cape Town’s water system become more resilient to the physical, social, and economic challenges of the present and future. Apart from advancing thought leadership on the topic of water system resilience, the resulting practical recommendations and technical, multi-disciplinary resources will inform the development of Cape Town’s Resilience Strategy.

###

For further information, please contact:

Nicole Bohrer-Kaplan
NBohrer@100RC.org / 646-612-7177

About 100 Resilient Cities—Pioneered by The Rockefeller Foundation 

100 Resilient Cities – Pioneered by The Rockefeller Foundation (100RC) helps cities around the world become more resilient to social, economic, and physical challenges that are a growing part of the 21st century. 100RC provides this assistance through: funding for a Chief Resilience Officer in each of our cities who will lead the resilience efforts; resources for drafting a resilience strategy; access to private sector, public sector, academic, and NGO resilience tools; and membership in a global network of peer cities to share best practices and challenges. For more information, visit: www.100ResilientCities.org.

Copyright@2018 Addis Ababa City Resilience Project Office | All Rights Reserved